Christmas Guest/Helen Stiner Rice/Translation Alem Hailu G/K/Amharic (የ ገና እንግዳ) Poem by Alem Hailu Gabre Kristos

Christmas Guest/Helen Stiner Rice/Translation Alem Hailu G/K/Amharic (የ ገና እንግዳ)



የሆነ ቀን ነው ነገሩ የተከሰተው፣
ዓመቱ ተገባዶ ሲሰናበት፣
ደርቦ ካባ ፀዓዳ ወተት!
ሊጎበኙት መጡ ሁለት ጎረቤቶች፣
የኮናርድ አብሮአደጎች፣
ወና ሆኖ ተዳክሞ አገኙት ሱቁን፣
ገርጥቶ ተቆራምዶ እሱን!
ተወት አድርጎ የሚሰፋውን፣
ፈልጎ እንዲሰሙ የሚለውን፣
'ባንጀሮቼ አድምጡኝ፣
ዛሬ በማለዳ
አውራ ዶሮ ሌሊቱን
በጩከት ሲሸኝ፣
ጌታ በሕልሜ ተገልፆ
ይህን አለኝ
‘እመጣለሁ ቤትህ፣ ልጎበኝህ! '
ይኸው አለሁ
ያለፋታ ቤቴ ውስጥ እንዲሁ ስመላለስ፣
የፅድ ዝንጣፊ ስቆርጥ ስነሰንስ፣
ጠረጴዛውን ስዘረጋ - ስጎትት ሳስጠጋ፣
የሻይ ጀበናውን ስፍቅ - እስኪያብረቀርቅ!
በመለጠቅ አድርጊያለሁ ደማቅ፣
ባለቀይ ኳስ ገመድ፣
በሸሪራዎቹ ቁልቁል ተንጠላጥሎ፣
በየአቅጣጫው እንዲወርድ!
እናም እስኪገለጥልኝ ጌታ፣
እየተጠባበቅኩ ነው የእግሩን ኮሽታ፣
ሲገለጽ በሬን ከፍቼ፣
ፊቱን ለማየት ጓጉቼ፣
ትንሽ ተጠግቼ! '
ባልንጀሮቹ የሚለውን ሰምተውት፣
ሄዱ ቤታቸው ብቻውን ትተውት!
እሱ እንደው፣
በጣም የተደሰተበት ወቅት ነው፡፡
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቤተሰቦቹ
ተራ በተራ ሞተዋል፣
ኮናርድም ብዙ ብቸኛ ቀዝቃዛ
ገናዎች አሳልፏል!
ሆኖም ነበረው ትልቅ እምነት፣
በእንግድነት ስለሚገኝለት፣
ጌታ ያቺን ቀን፣ ቤቱን እንደሚያደምቅለት!
ነበር ተደስቶ፣
የሚያደምጥ ጆሮውን አንቅቶ!
ድምፅ ሰምቶ ቀጥ አለ በቅፅበት፣
መጥቶ እንደው ጌታ ድንገት፣
ለብርቱ ፀሎቱ ምላሽ ለመስጠት!
ወደ መስኮቱ ሮጦ ሲጠጋ
በዚያ በረዶ የሸፈነው፣
አስፋልት ላይ ያየው፣
ብትቶ የለበሰ ለማኝን ነው -
ምስኪን፣ አፍንጫው የተገነጠለ፣
ጫማ፣ የተጫማ!
'ደንዝዞ ቆስሎ ይሆናል እግርህ፣
ጫማ አለ ሱቄ በልክህ፣
ግባ ልስጥህ-
ኮትም የሚያሞቅህ! '
ለማኙ የሚፈልገውን አግኝቶ፣
ወጥቶ ሄደ ረክቶ!
ኮናርድ ግን
በመገረም ጌታ ለምን እንደቆየ፣
ሰዓቱን አየ፡፡
ከዚያም ቆመ ግራ በመጋባት፣
መቆየት እንዳለበት፣
ምን ያህል ተጨማሪ ሰዓት?
ግን ድንገት፣
ኳኳ የሚል ድምጽ ሰምቶ፣
በሩን ከፈተ ወደዚያ አምርቶ፡፡
ግን እንደገና አየ ሌላ እንግዳ፣
የፈለገች ለመዝለቅ ከጓዳ፣
አረጋዊት የጎበጠች፣
ቲውቢት የደረበች፣
ትንሽ ጭራሮ ከጀርባዋ የሸከፈች፣
እናም እረፍት የማድረጊያ ቦታ ጠየቀች፡፡
ለታላቁ እንግዳ በቀር፣
ሌላ ስፍራ አልነበር!
ጥያቄዋ የመማፀን ድምፀት፣
ነበር የተጫነበት፣
ኮናርድ ‘ቤት ለእንግዳ' ብሏት፣
ሻይ አፍልቶላት
ከጠረጴዛው እንድታርፍ ጋብዟት፣
እነሆ ጠጪ አላት፡፡
ግን እሷን እንደሸኘ አዘነ፣
ሰዓቱ እያለፈ ስለሆነ!
ደሞም ጌታን ሲጠብቀው ስለቀረ፣
መልክቱን በደንብ ማድመጡን ተጠራጠረ!
ሀዘን ገብቶት ሲያቅማማ፣
ሌላ ድምፅ ሰማ!
'እባክህ እርዳኝ
የት ነው ያለሁት? '
ዳግም የደግነት በሩን ሲከፍት፣
ለሶስተኛ ጊዜ አለው ክፍት!
መንገድ የጠፋት ልጅ ነበረች፣
ሳታስበው በገና ቀን
ከቤተሰቧ ተለይታ የሄደች!
የኮናርድ ልብን ሀዘን ገባው፣
ቢሆንም ልጅቷን ማፅናናት እንዳለበት ተሰማው!
'ግቢ ልጄ' ብሏት እንባዋን አበሰላት፣
እንዳትረበሽ አረጋጋት፣
ቤቷም ድረስ ሸኛት!
ተመልሶ ሲገባ፣
ወደ ክፍሉ ሞገስ አልባ
'በቃ አለቀ ደቀቀ
ቀኑም ተጠናቀቀ! ' ብሎ ተሳቀቀ፡፡
ያም ሆኖ
ስሜቱ እንደቀዘቀዘ፣
መፀለይ ያዘ!
'ጌታ ለምን ዘገየህ፣
ቤቴ እንዳትመጣ ምን ያዘህ? '
እያለ ቅሬታ ሲያሰማ
እንግዳ ድምፅ ሰማ
‘ጭንቅላትህን ወደ ላይ አንሳ፣
እኔ እንደው ቃሌን አረሳ!
በደጅህ በምድራኳ፣
በጥላዬ ተጠግቼ በርህን ላንኳኳ፣
ሶስቴ ጎብኝቼሀለሁ ዛሬእንኳ!
እኔ ለማኙ ነበርኩ፣
የቀረብኩህ ብትቶ እንደደረብኩ!
ደሞም ከድካሟ የታደግካት፣ ባልቴት፣
በመጠለያ አልባው ውርጫማው መንገድ፣
ለሆንካትም ልጅ ዘመድ'
(በሔለን ስቲነር ራይስ)
I think this is the best poem about Christmas, we have to support the needy. Google and read Helen Stiner Rice's poem Christmas Guest.The Americans call her an Ambassador of Sunshine for her uplifting poem.
© Alem Hailu Gabre Kristos christmas • love • sad • friendship • society

Christmas Guest/Helen Stiner Rice/Translation Alem Hailu G/K/Amharic (የ ገና እንግዳ)
Tuesday, November 28, 2017
Topic(s) of this poem: christmas
POET'S NOTES ABOUT THE POEM
I think this is the best poem about Christmas, we have to support the needy. Google and read Helen Stiner Rice's poem Christmas Guest.The Americans call her an Ambassador of Sunshine for her uplifting poems.
COMMENTS OF THE POEM
READ THIS POEM IN OTHER LANGUAGES
Close
Error Success