ነበረ ስላንቺ ሐሣቤ ሚቀና
ብዕሬ ሚሠላ
እብሪት ያደደረው ልቤ የሚላላ
ናፍቆት የደቆሰው ውስጤ የሚንሰራራ
ጭንቀት የተጣባው መንፈሤ የሚገራ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡[-]✿✿✿፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ዛሬ ግን ተረሳኝ ለፍቅርሽ ያዜምኩት
ግጥሙ ተዘነጋኝ በቃሌ የያዝኩት
ቅላፄውም ጠፋኝ ዳዊቴ ያረኩት
መራቅሽ ሲቀመር፡ ተስፋዬ እየሳሳ
በፍቅርሽ መቁረጡን አስጨከነኝሳ
(ላም አለኝ በሠማይ አሳሰበኝሳ)
አንቴናውን ያጣ ቢራቢሮ ሳለሁ
አበባው ላይ ማረፍ እንዴት እችላለሁ?
This poem has not been translated into any other language yet.
I would like to translate this poem